የአማራ ክልል አሥተዳደር ጉዳዮች ክላስተር የተቋማትን የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ ዝግጅት ግምገማዊ ውይይት በባሕር ዳር ከተማ ተካሄደ።
ባሕር ዳር: ሐምሌ 18/2016 ዓ.ም በግምገማዊ ውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ ብርሃኑ ጎሽም እንዳሉት ክልሉ በገጠመው የጸጥታ ችግር የፍትሕ ባለሙያዎች ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሰው መሥራት እንዳልቻሉ ተናግረዋል። ፍትሕ ፈላጊውም ሆነ ማንኛውም ሰው በሚፈልገው ልክ መንቀሳቀስ ባለመቻሉ በማህበራዊ፣ በምጣኔ ሃብታዊ፣ ፖለቲካዊ እና በሥነ ልቦና ደረጃ ጉዳት ደርሷል ነው ያሉት።
አቶ ብርሃኑ አክለውም በፍርድ ቤቶች ደረጃ በጸጥታው ችግር በርካታ ፋይሎች ቢበላሹም በችግር ውስጥ ሆነውም ጥሩ ሥራዎችን ማከናወናቸውን ተናግረዋል። ኀበረተሰቡም ለሰላም ዘብ እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።
